ወደ እግዚአብሔር መቅረብ
"... ወደ እግዚአብሔር ቅረቡ ወደ እናንተም ይቀርባል::" ያዕ 4:8
ወደ እግዚአብሔር እንዴት እንቅረብ?
ወደ እግዚአብሔር እንዴት እንቅረብ?
1. በምሥጋናና በውዳሴ መዝ. (34): 1፥ ዕብ.13:15
ሁልጊዜ ወደ እግዚአብሄር ፊት በምሥጋና ልንቀርብ ይገባል::
ምሥጋና የምናቀርበው ከጌታ ለተቀበልናቸው ነገሮች ሁሉ ነው:: ስለጤንነታችን፥ ስለምንበላው ምግብ፥ ስለምንተነፍሰው አየር፥ ስለ ሰጠን ሥራ፥ ስለ ቤተሰባችን፥ ስለ መዳናችንና ስለ ሌሎችም ስለተቀበልናቸው ነገሮች ጌታን ልናመሰግን ይገባል:: በግል የአምልኮ ህይወታችን ምሥጋናን ልንለማመድ ይገባል::
ውዳሴ ማለት የእግዚአብሄርን ታላቅነት መናገር ማለት ነው::እግዚአብሄርን ታላቅ ነህ ፥ ኅያል ነህ ፥ ሁሉን ቻይ ነህ ፥ የሚመስልህ የለም ፥ ቅዱስ ነህ፥ የነገሥታት ንጉሥ ነህ ፥ የአማልክት አምላክ ነህ፥ የጌቶች ጌታ ነህ ፥ አዋቂ ነህ፥ብርቱ ነህ፥የሠራዊት ጌታ ነህ ፥ የኅያላን ሁሉ ኅያል ነህ ፥ ሠማይን የሠራህ ፥ የምድር ዳርቻ ፈጣሪ ፥ፀሀይንና ጨረቃን የፈጠርክ ፥ ከዋክብትን በስማቸው የምትጠራ ፥ የኤርትራን ባህር የከፈልክ ህዝብህን ያሻገርክ ፥ አልፋና ኦሜጋ ነህ ፥ዘላለማዊ ነህ ፥ ማስተዋልህ አይመረመርም፥ ጠቢብ ነህ ስንለውና ታላላቅ ሥራዎቹን ስንናገር እያወደስነው ነው:: ይህንን ሁልጊዜ ልንለማመድ ይገባል:: የተፈጠርነው ጌታን ለማምለክ ነው:: ለመብላትና ለመጠጣት አልተፈጠርንም:: የምንበላውና የምንጠጣው ለመኖር ነው:: የምንኖረው ግን ጌታን ለማምለክ ነው:: እግዚአብሄርን ማመሥገንና ማወደስ አንዱ (ብቸኛው ባይሆንም) የአምልኮአችን መገለጫ ነው::
ምሥጋና የምናቀርበው ከጌታ ለተቀበልናቸው ነገሮች ሁሉ ነው:: ስለጤንነታችን፥ ስለምንበላው ምግብ፥ ስለምንተነፍሰው አየር፥ ስለ ሰጠን ሥራ፥ ስለ ቤተሰባችን፥ ስለ መዳናችንና ስለ ሌሎችም ስለተቀበልናቸው ነገሮች ጌታን ልናመሰግን ይገባል:: በግል የአምልኮ ህይወታችን ምሥጋናን ልንለማመድ ይገባል::
ውዳሴ ማለት የእግዚአብሄርን ታላቅነት መናገር ማለት ነው::እግዚአብሄርን ታላቅ ነህ ፥ ኅያል ነህ ፥ ሁሉን ቻይ ነህ ፥ የሚመስልህ የለም ፥ ቅዱስ ነህ፥ የነገሥታት ንጉሥ ነህ ፥ የአማልክት አምላክ ነህ፥ የጌቶች ጌታ ነህ ፥ አዋቂ ነህ፥ብርቱ ነህ፥የሠራዊት ጌታ ነህ ፥ የኅያላን ሁሉ ኅያል ነህ ፥ ሠማይን የሠራህ ፥ የምድር ዳርቻ ፈጣሪ ፥ፀሀይንና ጨረቃን የፈጠርክ ፥ ከዋክብትን በስማቸው የምትጠራ ፥ የኤርትራን ባህር የከፈልክ ህዝብህን ያሻገርክ ፥ አልፋና ኦሜጋ ነህ ፥ዘላለማዊ ነህ ፥ ማስተዋልህ አይመረመርም፥ ጠቢብ ነህ ስንለውና ታላላቅ ሥራዎቹን ስንናገር እያወደስነው ነው:: ይህንን ሁልጊዜ ልንለማመድ ይገባል:: የተፈጠርነው ጌታን ለማምለክ ነው:: ለመብላትና ለመጠጣት አልተፈጠርንም:: የምንበላውና የምንጠጣው ለመኖር ነው:: የምንኖረው ግን ጌታን ለማምለክ ነው:: እግዚአብሄርን ማመሥገንና ማወደስ አንዱ (ብቸኛው ባይሆንም) የአምልኮአችን መገለጫ ነው::
2. ቃሉን ማንበብ ፥ መስማት ፥ ማጥናት ፥ ማሰላሰልና በቃል ማስታወስ
የእግዚአብሄር ቃል እምነትን (እርግጠኛ ተስፋ) በውስጣችን ይፈጥራል አእምሮን ያድሳል የአስተሳስብ ቅድስና ያመጣል:: ስንጸልይ ከጌታ ኅይል እናገኛለን:: ቃሉን ስናነብ ግን የአስተሳሰብ ለውጥ እናመጣለን:: እንደ እግዚአብሄር ማሰብ እንጀምራለን:: እግዚአብሄር ቃል የእግዚአብሄርን አሳብና ፍላጎት ይናገራል:: በየዕለቱ 4 ምዕራፍ በማንበብ መጽሐፍ ቅዱሳችንን በየዓመቱ አንዴ መጨረስ እንችላለን:: ቢሊ ገርሃም ከ150 ጊዜ በላይ መጽሐፍ ቅዱስን አንብበዋል:: በመሆኑም እግዚአብሔር የተጠቀመባቸው የወንጌል
አገልጋይ ለመሆን በቅተዋል:: ጆርጅ ሙለር የተባሉ የእግዚአብሔር ሰው ደግሞ ከ300 ጊዜ በላይ መጽሐፍ ቅዱስን አንብበዋል:: በመሆኑም የእምነት ሐዋርያ ለመባል በቅተዋል:: በዘመናቸው
ወደ 2000 የሚጠጉ ወላጅ ዐልባ ህፃናትን በእምነት በተገኘ በጀት አሳድገው ለወግ ለማዕረግ አብቅተዋል::
3. በጸሎት ወደ
ፊቱ
መቅረብ
በየዕለቱ በጸሎት ወደ ጌታ መቅረብ አለብን:: ጌታ ኢየሱስ ወደ አባቱ ፊት መቅረብ እጅግ ደስ የሚያሰኘው ነገር ነበር:: እኛም ወደ አፍቃሪአችን ጌታ ፊት መቅረብ ልንናፍቅ ይገባል:: ለልመና ብቻ ልንቀርብ አይገባም:: ፍቅራችንን ለመግለጽ ወደ ፊቱ መቅረብ አለብን:: ጌታ ሆይ እወድሃለሁ ልንለው ይገባል:: በጸሎት ወደ ፊቱ ስንቀርብ ጌታ መንፈሱንና ኅይሉን ይሞላናል:: ክብሩን ያሳየናል::ክብሩን ስናይ እንጠግባለን:: በየዕለቱ ቢያንስ ለአንድ ሰዓት የጸሎት ጊዜ ቢኖረን መልካም ነው:: ወደ ፈተና እንዳትገቡ ትጉና ጸልዩ ብሏል ጌታ::
4. እግዚአብሔርን ማሰብና ማሰላሰል
ሁልጊዜ እግዚአብሔርን በፊቴ አየዋለሁ በቀኜ ነውና አልታወክም:: ስለዚህ ልቤን ደስ አለው ምላሴም ሐሴት አደረገች:: መዝ. (16): 8 ጌታንና ምህረቱን ቸርነቱንና ታላቅነቱን ማሰብ ወደ እግዚአብሄር እንድንጠጋ ያደርገናል::
5. ከቅዱሳን ጋር
ህብረት ማድረግ መዝ. (133): 1-3
ቅዱሳን የጌታ አካል ስለሆንን በጌታ ህብረት ስናደርግ የጌታን ጸጋ እንከፋፈላለን:: ይህም ወደ እግዚአብሄር እንድንጠጋ ያደርገናል:: እግዚአብሄር በቤተ ክርስቲያን (በቅዱሳን መሰባሰብ በኩል) በኩል ነው ፀጋውን የሚለቀው:: ከቅዱሳን ጋር ጌታን ማምለክ መጸለይ ማገልገል ከጌታ ጋር የጠበቀ ህብረት እንዲኖረን ይረዳል:: ጌታ አብዝቶ ይባርከን!!
በወ/ም ተድላ ሲማ
No comments:
Post a Comment